በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ማንም ሰው ሃሳቡን በሰላማዊ መንገድ በመግለጹ ምክንያት መሞት የለበትም"ለስሊ ሪድ


በኢትዮጵያ የዩኤስአይዲ ዳይሬክተር ለስሊ ሪድ
በኢትዮጵያ የዩኤስአይዲ ዳይሬክተር ለስሊ ሪድ

ማንም ሠው ሃሳቡን በሰላማዊ መንገድ በመግለጹ ምክንያት መሞት የለበትም ሲሉ ስለ ሰሞኑ የኦሮምያ እና የአማራ ሰልፎች የተናገሩት በኢትዮጵያ የዩኤስአይዲ ዳይሬክተር ለስሊ ሪድ አስታወቁ።

መንግሥት እና አደባባይ የወጡ ሰልፈኞች ለመነጋገር ሰላማዊ መንገድ እንዲፈልጉ እርስ በእርሳቸው እንዲደማመጡም አሳስበዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ዓለምአቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት(የዩኤስአይዲ) የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ለስሊ ሪድ ስለ ኢትዮጵያ የተቃውሞ ሰልፎች ያነሱት በአዲስ አበባ በተከበረው እና በርካታ እንግዶች በተገኙበት ዓለምአቀፍ በዓል ላይ ነው። በዚህ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊነት ቀን በሚከበርበት በዓል ላይ ንግግር ያደረጉት ሚስ ለስሊ ንግግራቸው የጀመሩት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑት ፓትሪሻ ሃስላክ መገኘት አለመቻላቸውንና የእሳቸውን ሰላምታ በመግለጽ ነው።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

"ማንም ሰው ሃሳቡን በሰላማዊ መንገድ በመግለጹ ምክንያት መሞት የለበትም"ለስሊ ሪድ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:28 0:00

XS
SM
MD
LG