በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ደቡብ ኮሪያ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ አደረጉ


ፎቶ ፋይል፦ የዩናይትድ ስቴትስ እና ደቡብ ኮሪያ ወታደሮች በደቡብ ኮሪያ ኢቻን አቅራቢያ በሚገኘው የኮሪያ የጦር ት/ቤት እአአ ታኅሣስ 22/2023
ፎቶ ፋይል፦ የዩናይትድ ስቴትስ እና ደቡብ ኮሪያ ወታደሮች በደቡብ ኮሪያ ኢቻን አቅራቢያ በሚገኘው የኮሪያ የጦር ት/ቤት እአአ ታኅሣስ 22/2023

ዩናይትድ ስቴትስ እና ደቡብ ኮሪያ በዚህ አውሮፓውያን ዓመት የመጀመሪያቸው የሆነውን የጋራ ልዩ ኃይል ወታደራዊ ልምምድ አድርገዋል።

የደቡብ ኮሪያ ጦር ዛሬ ዓርብ እንዳስታወቀው እኤአ ጥር 31 የተደረገው ልምምድ የተካሄደው በኮሪያ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው የሰሜን ደቡብ ኮሪያ ፖቼዮን ከተማ ውስጥ ነው።

ዶን ጉ የተባሉት አንድ የደቡብ ኮሪያ መኮንን ለአሜሪካ ድምጽ እንደተናገሩት "የአሁን ልምምድ የደቡብ ኮሪያ እና ዩናይትድ ስቴትስ ልዩ ኃይሎች እንዲቧደኑና እና የተቀናጀ ልዩ ኦፕሬሽን የማካሄድ አቅማቸውን እንዲያጠናክሩ እድል ሰጥቷቸዋል። ወደፊትም በጠላት ላይ የበላይነትን ለመቀዳጀት የልዩ ኃያሎች ወታደራዊ ግዳጆችንን በሚያገሎበቱ ልምምዶች አማካይነት የራሳችንን አቅም ማጠናከሩን እንቀጥላለን፡፡” ብለዋል፡፡

ልምምዱ የተኩስ፣ ልዩ አሰሳ እና ወደ ጠላት ኃይል ሰርጎ የመግባት ልምምዶችን ያካተተ እንደነበር ሲገለጽ የአጋር አካላት በጋራ የሚያደርጓቸውን ወታደራዊ ግዳጆችን ለማጠናከርና በጋራ ለመስራት ያላቸውን አቅም ለማሳደግ ያለመ ልምምድ መሆኑም ተገልጿል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG