በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነጮቹ ገበሬዎች መሬታቸውን እየተቀሙ ይገደላሉ" - ፕሬዚዳንት ትረምፕ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነጮቹ ገበሬዎች መሬታቸውን እየተቀሙ ይገደላሉ ብለው በትዊተር መፃፋቸው ተከትሎ የዘር ክፍፍል እየቀሰቀሱ ናቸው ስትል ደቡብ አፍሪካ ወነጀለቻቸው።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነጮቹ ገበሬዎች መሬታቸውን እየተቀሙ ይገደላሉ ብለው በትዊተር መፃፋቸው ተከትሎ የዘር ክፍፍል እየቀሰቀሱ ናቸው ስትል ደቡብ አፍሪካ ወነጀለቻቸው።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ በዋይት ኃውስ ኦፊሴላዊ ትዊተራቸው ባለፈው ማከሰኞ ባወጡት ቃል ደቡብ አፍሪካ ውስጥ የሚካሄደውን የመሬት ነጠቃ እና በስፋት የሚፈፀመውን ግድያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፓምፔዎ በቅርበት ይከታተሉ ሲል ጠይቀዋል።

ፕሬዚዳንቱ ይህን ያሉት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ያወጡትን አዲስ የመሬት ይዞታ ለውጥ ዕቅድ ተከትሎ ነው።

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት በሰጠው ምላሽ የሚስተር ትረምፕን ቃል አገራችንን ለመከፋፈል እና ያለፈውን የቅኝ አገዛዝ ዘመን ለማስታወስ የየታለመ ጠባብ አመለካከት ፈፁሞ አንቀበልም ብሉዋል። አስከትሎም ደቡብ አፍሪካ የመሬት ይዞታ ለውጥ ርምጃዎቹዋን ሃገረችንን በማይከፋፍልመንገድ በጥንቃቄ ታካሂዳለች ሲል አስታውቁዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG