በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አሜሪካና ኢትዮጵያ ግልፅ ንግግሮችን ለማድረግ ተስማሙ


የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አርማ
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አርማ

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢትዮጵያ አስተዳደርና ሰብዓዊ መብቶችን በሚመለከቱ ስፋት ያላቸው ጉዳዮች ላይ በግልፅነት ለመወያያት መስማማታቸውን አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የዴሞክራሲ፣ የሰብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪና በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ የሚመሩት የሁለቱ ሃገሮች ቡድኖች ዛሬ ያደረጓቸው ውይይቶች የኢትዮጵያ መንግሥት የሃገሪቱን የምርጫ አያያዝ ለማሻሻል የገባውን ቃል እንዲገፋበት ማሳሰብን ጨምሮ ስፋት ባላቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ኤምባሲው አክሎ አመልክቷል፡፡

በተጨማሪም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወቅት ሕገ-መንግሥታዊ መብቶች እንዲከበሩ፣ ለውይይት ሁኔታዎች አንዲመቻቹ፣ ጠንካራ መገናኛ ብዙኃን እንዲኖሩም ውይይቱ ትኩረት አድርጎ መነጋገሩን መግለጫው ጠቁሟል፡፡

መሠረታዊ ነፃነቶች እየተከበሩ የጥላቻ ንግግሮችን ለመቆጣጠር እንዲቻልና የሲቪል ማኅበረሰብ አስፈላጊ ጫና ለመልካም አስተዳደርና ለዓመታዊው የዩናይትድ ስቴትስ የሰብዓዊ መብቶች ሪፖርት ያለውን ጥቅም አንስተው የሁለቱ ሀገሮች ቡድኖች መክረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂሩት ዘመዴነህና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ ጉዳይ ፈፃሚ ፒተር ቨርማን ተባባሪ ሊቀመንበርነት የተመራው ይህ ሰባተኛው የሥራ ቡድን ስብስባ ወደፊት በሚያደርጓቸው ውይይቶች በግልፅነት ለመነጋገር መስማማታቸውን የኤምባሲው መግለጫ አመልክቷል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

አሜሪካና ኢትዮጵያ ግልፅ ንግግሮችን ለማድረግ ተስማ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:31 0:00

XS
SM
MD
LG