በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ጠ/ሚኒስትር አብይ እያካሄዱ ያለውን ለውጥ ዩናይትድ ስቴትስ አደነቀች


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ እያካሄዱ ያለው ለውጥ ከፍጥነትም ሆነ ከይዘት አንፃር የሚደነቅ መሆኑን ዩናይትድ ስቴትስ አስታውቃለች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ እያካሄዱ ያለው ለውጥ ከፍጥነትም ሆነ ከይዘት አንፃር የሚደነቅ መሆኑን ዩናይትድ ስቴትስ አስታውቃለች፡፡ ለእነዚህ የለውጥ ርምጃዎች መሳካት ሀገራቸው በአጋርነት መሥራት እንደምትፈልግም በኢትዮጵያ የአሜሪካ ቃል አቀባይ ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድም ከአንድ ሳምንት በኋላ ወደ ዋሺንግተን ያመራሉ፣ በዚያም ጉብኝት መልካሙን እንመኝላቸዋለን ያሉት ቃል አቀባዩ ኒኮላስ ባርኔት፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ጋር የሚደረግ ውይይት ሰለመኖሩ ግን አልጠቀሱም፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሳምንታት በፊት በሰጠው መግለጫ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሜሪካ ጉዞ ዓላማ፣ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር መወያየት ብቻ መሆኑን ጠቁሞ ነበር፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

ጠ/ሚኒስትር አብይ እያካሄዱ ያለውን ለውጥ ዩናይትድ ስቴትስ አደነቀች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:48 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG