በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዚህ ዓመት 12 ሺህ ደቡብ ሱዳናዊያን ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል መባሉን ዩኤንኤችሲአር አስተባበለ


የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር
የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር




please wait

No media source currently available

0:00 0:07:01 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

በያዝነው የአውሮፓዊያን ዓመት ከደቡብ ሱዳን እየተሰደዱ ወደ አጎራባች ሃገሮች የገቡት ደቡብ ሱዳናዊያን ቁጥር ከ19 ሺህ እንደሚበልጥ የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን እየጠቀሱ ቢዘግቡም የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር የኢትዮጵያ ቢሮ የተጠቀሰው ቁጥር ትክክል አለመሆኑን አስታውቋል፡፡

ዘገባውን የመንግሥታቱን ድርጅት ጠቅሰው ያሠራጩት ራዲዮ ባኺታ ኤፍ ኤም የሚባል የደቡብ ሱዳን ራዲዮ ጣቢያ፣ ሮይተርስ እና አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ናቸው፡፡

በዚህ ዓመት ማለትም ባለፉት አምስት ወራት ብቻ ከደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የፈለሰው ስደተኛ 12 ሺህ እንደደርስና ከሚያዝያ 29 እስከ ግንቦት 16/2005 ዓ.ም ባሉት ሁለት ሣምንታት ተኩል ጊዜ ውስጥ አራት ሺህ ስደተኛ መግባቱን ዘገባዎቹ ጠቁመዋል፡፡

ስለሁኔታውና ስለዘገባዎቹም ለቪኦኤ መግለጫ የሰጡት የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር የኢትዮጵያ ቢሮ ቃልአቀባይ አቶ ክሱት ገብረእግዚአብሔር ከደቡብ ሱዳን ወደ 15 ሺህ የሚሆኑ ስደተኞች ወደኢትዮጵያ የገቡት ባለፈው የአውሮፓዊያን ዓመት መሁኑን ጠቁመው በዚህ ዓመት ደቡብ ሱዳን ጆንግሌይ ክፍለሃገር ውስጥ ግጭት ከተነሣ ወዲህ የገቡት ሰዎች ቁጥር ከስድስት መቶ እንደማይበልጥ አቶ ክሱት አመልክተዋል፡፡

በደቡብ ሱዳን ጆንግሌይ ግዛት ውስጥ ይህ በቅርቡ ተነሣ የተባለ ግጭትና አለመረጋጋቱ የሃገሪቱ መንግሥት በአባባቢው የጀመረውን የነዳጅ ፍለጋ ሥራ ማስተጓጎሉ ተነግሯል፡፡

ለተጨማሪና ዝርዝር የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG