በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የተመድ የሰብዓዊ ጉዳይ ምክትል ኃላፊ በኤርትራ


የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳይ ምክትል ዋና ፀኃፊ አርሰላ ሙለር ከትናንት ወድያ ሰኞና ማክሰኞ ኤርትራ ጉብኝት አካሂደዋል ሲል የኤርትራ የማስታወቅያ ሚኒስቴር መግለጫ ገልጿል።

የሰብዓዊ ጉዳይ ምክትል ዋና ፀኃፊ አርሰላ ሙለር በጉብኝታቸው ወቅት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቲር አሚና ኑርሑሴን፣ ከእርሻ ሚኒስትር አርፋነ በርሀና ከሌሎችም ባለስልጣኖች ጋር ተገኛተው መነጋገራቸውን መግለጫው ጠቅሷል።

በስብሰባቸው ወቅት የኤርትራ መንግሥት ከተባበሩት መንግሥታ ትድርጅት ጋር በመተባበር ስለሚያከናውናቸው መርኃ ግብሮች ሃሳብ ተለዋውጠዋል። ለወደፊት ስለሚደረገው የልማት ትብብርም ተነጋግረዋል ይላል የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ያወጣው መግለጫ።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG