ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ሰኞ በበዓለ ሲመት ሥነ ሥርዐታቸው ላይ ባደረጉት ንግግር "የጋራ አስተሳሰብ አብዮት" እንዲኖር ጠይቀዋል። 47ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ትላንት የፈፀሙት ቃለ መሐላ እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር በ2020 ለሁለተኛ የሥልጣን ዘመን ባደረጉት ፉክክር በጆ ባይደን ከተሸነፉ በኋላ አስደናቂ በኾነ መልኩ ወደ ሥልጣን መመለሳቸውን ያሳያል። የዋይት ኃውስ ዘጋቢ ዊዳኩስዋራ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
አዲሱ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "የጋራ አስተሳሰብ አብዮት" እንዲኖር ጠየቁ
- ቪኦኤ ዜና
መድረክ / ፎረም