በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሕወሓት ሊቀመንበሩን አነሣ

ሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ - ሕወሐት ሊቀመንበሩን ከሥልጣን አነሣ። አዜብ መስፍን ከማዕከላዊ ኮሚቴው ታገዱ።

ሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ - ሕወሐት ሊቀመንበሩን ከሥልጣን አነሣ። ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከማዕከላዊ ኮሚቴው ታገዱ።

ከአቶ መለስ ዜናዊ ሕልፈት ወዲህ ሕወሐትን በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን አቶ አባይ ወልዱን ከኃላፊነትና ከሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ማንሳቱን የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ማምሻውን አስታውቋል።

አቶ አባይ ወልዱ በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት እንደሚቀጥሉ ማምሻውን በሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን የተነበበው የፓርቲው መግለጫ አመልክቷል።

በተጨማሪም የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት የቀድሞዪቱ ቀዳሚት እመቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ከማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ታግደው እንዲቆዩ መወሰኑም ተገልጿል።

በተመሣሣይ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የነበሩት አቶ በየነ ምክሩ ደግሞ ወደ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ዝቅ ብለው እንዲሠሩ መወሰኑም ተገልጿል። ስማቸው ላልተገለፀ ሁለት የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትም ማስጠንቀቂያ መሰጠቱም ታውቋል።

የፓርቲው ሂስና ግለሂስ መቀጠሉን፣ የአመራር መልሶ ማደራጀትም እንደሚካሄድ ይኸው የሕወሐት ማዕከላዊ ኮሚቴ መግለጫ አመልክቷል።

  • 16x9 Image

    እስክንድር ፍሬው

This item is part of

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG