በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቤሩቱ ወደብ ፍንዳታ ታሳሪዎች እንዲፈቱ የሊባኖስ ከፍተኛ አቃቤ ሕግ አዘዙ


ፎቶ ፋይል፦ በቤሩት ወደብ ላይ የደረሰው ፍንዳታ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020
ፎቶ ፋይል፦ በቤሩት ወደብ ላይ የደረሰው ፍንዳታ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020

የሊባኖሱ ከፍተኛ አቃቤ ህግ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2020 በቤሩት ወደብ ላይ ከደረሰው ፍንዳታ ጋር በተያያዘ በተደረገው ምርመራ በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙት ታሳሪዎች እንዲለቀቁ አዘው ምርመራውን ይመሩ በነበሩት ዳኛ ላይ ክስ አቅርበዋል።

ዋና አቃቤ ሕግ ግህሳን ኦዩይዲት በትናንትናው ዕለት የወሰዱት እርምጃ ለዓመታት ሳይንቀሳቀስ ለቆየው ምርመራ ሌላ ኪሳራ ተደርጎ ታይቷል።

ምርመራው ሀገሪቱን ታይቶ ከማይታወቅ የኢኮኖሚ ውድቀት ውስጥ ባስገባው እና በሙስና እና በብልሹ አስተዳደር በተተበተበው የሊባኖስን ገዥ ልሂቅ የመናድ አደጋ ሥጋት አሳድሯል።

የአቃቤ ሕጉ ውሳኔው የተሰማው ዳኛው ታሬክ ቢታር ከፍተኛ ውድመት ባደረሰው ፍንዳታ ላይ ተቋርጦ የነበረውን ምርመራ ዳግም ማንቀሳቀስ ከጀመሩ በኋላ ነው።

የክስ ሂደቱ የተንቀሳቀሰው ዋናው አቃቤ ህግ ጨምሮ በምርመራው የተከሰሱ ፖለቲከኞች ያነሷቸውን ሕግ ነክ ጥያቄዎች ተከትሎ ለአስራ ሦስት ወራት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ነው።

XS
SM
MD
LG