No media source currently available
“አገራዊው ምርጫው በ2013 ዓ.ም እንዲካሄድ” ሲል ፓርላማው ያስተላለፈው ውሳኔ “በሕገወጥ መንግሥት እንዲተገበረ የታቀደ እና ተቀባይነት የሌለው ነው” ሲል የትግራይ ክልል ተቃወመው። አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በበኩላቸው፤ በፌደሬሽን ምክር ቤት የሥልጣን ዕድሜው የተራዘመለት ሕጋዊ መንግሥት እንዳለ በመግለፅ ፤“በእልህና በስሜታዊነት ተነሳስቶ ያልተገባ ነገር መናገር ተገቢ አይለምም” ብለዋል።