በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያዊው ሄግ ላይ በቀይ ሽብር ተከሰሱ


የሄግ ፍርድ ቤት
የሄግ ፍርድ ቤት

ኢትዮጵያ ውስጥ በ1960ዎቹ መጨረሻ ላይ በተካሄደው ቀይ ሽብር ውስጥ እጃቸው አለ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ሆላንድ ውስጥ ተይዘው አንድ የሄግ ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ኢትዮጵያ ውስጥ በ1960ዎቹ መጨረሻ ላይ በተካሄደው ቀይ ሽብር ውስጥ እጃቸው አለ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ሆላንድ ውስጥ ተይዘው አንድ የሄግ ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ሮይተርስና የፈረንሣይ የዜና ወኪል - ኤኤፍፒ ባሠራጯቸው ዘገባዎች መሠረት እሸቱ ዓለሙ የሚባሉት የ63 ዓመት ዕድሜ ተጠርጣሪ በወቅቱ የሃገሪቱ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ተሹመው ጎጃም ክፍለ ሃገር ውስጥ በነበሩ ጊዜ በ197ዐ ዓ.ም. ሰባ አምስት ወጣት እሥረኞች እንዲገደሉ ትዕዛዝ ሰጥተዋል የሚል ክሥ ተመሥርቶባቸዋል።

ኢትዮጵያዊው ሄግ ላይ በቀይ ሽብር ተከሰሱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:59 0:00

ሆላንድ ውስጥ ጥገኝነት ጠይቀው ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት እዚያው እየኖሩ ያሉት እሸቱ ዓለሙ በተጨማሪም ከሁለት መቶ በሚበልጡ ሰዎች ላይ ጅምላ እሥራትና ማሳደድ በማካሄድ፣ እንዲሁም ኢሰብዓዊ አያያዝ በመፈፀም ተከስሰዋል።

አቶ እሸቱ የእምነት ክሕደት ቃላቸውን በችሎት ፊት በሰጡበት ወቅት የተከሰሱባቸውን አድራጎቶች እንዳልፈፀሙ ተናግረዋል።

አቶ እሸቱ በቀይ ሽብር ወቅት ፈፅመዋቸዋል ለተባሉ ጥፋቶች ጉዳዩን በሌሉበት ያየው የኢትዮጵያ ፍርድ ቤት የሞት ፍርድ አስተላልፎባቸው እንደነበረ የዜና አውታሮቹ ዘገባዎች ጠቁመዋል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኢትዮጵያዊው ሄግ ላይ በቀይ ሽብር ተከሰሱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:03 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG