በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ደቡብ አፍሪካ ውስጥ የደረሰው ከባድ የጎርፍ መጥለቅለቅ


የረዘመ ዝናብ እና የጎርፍ መጥለቅለቅን ተከትሎ የሰዎች መኖሪያ ቤቶች ጉዳት ደርሶበታል በንቱዙማ፣ ደርባን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ እአአ ሚያዚያ 12/2022
የረዘመ ዝናብ እና የጎርፍ መጥለቅለቅን ተከትሎ የሰዎች መኖሪያ ቤቶች ጉዳት ደርሶበታል በንቱዙማ፣ ደርባን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ እአአ ሚያዚያ 12/2022

ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በከባድ ዝናብ የተነሳ የተፈጠረው የጎርፍ መጥለቅለቅ ሦስት መቶ አርባ አንድ ሰዎች ሲሞቱ በብዙ ሺህ የተቆጠሩ ነዋሪዎች የመጠለያ ኤሌክትሪክ እና ውሃ ችግር ውስጥ ወድቀዋል።

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት በጎርፉ ለተጎዱት የሀገሪቱ ምስራቃዊ የጠረፍ አካባቢው ነዋሪዎች አስቸኳይ እርዳታ የሚውል ገንዘብ እንደሚለቅቅ አስታውቋል።

ፕሬዚዳንቱ ሲሪል ራማፎሳ የአጣዳፊ አደጋ ቀጣና ብለው ላወጁት አካባቢ ስድሳ ስምንት ነጥብ ሦስት ሚሊዮን ዶላር ለአስቸኳይ እርዳታ መመደቡን የገንዘብ ሚኒስቴሩ አስታውቆ፣ ተጨማሪ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ይመደባል ብሏል።

የክዋዙሉ ናታል ክፍለ ግዛት አስተዳዳሪ እንዳስታወቁት በጎርፍ አደጋው አርባ ሺህ ሰባት መቶ ሰው ጉዳት ላይ ወድቋል።

XS
SM
MD
LG