በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቀድሞ የጋቦን ፕሬዚዳንት ልጅ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ተያዙ


የቦንጎ የበኩር ልጅ ኑረዲን ቦንጎ ቫለንቲን
የቦንጎ የበኩር ልጅ ኑረዲን ቦንጎ ቫለንቲን

በቅርቡ በመፈንቅለ መንግሥት የተወገዱት የቀድሞ የጋቦን ፕሬዚዳንት አሊ ቦንጎ ኦንዲምባ ልጅና ሌሎች በርካታ ተባባሪዎች በሙስና ተከሰው በእስር ላይ እንደሚገኙ የአገሪቱ ዐቃቤ ህግ ዛሬ ረቡዕ ለኤኤፍፒ ተናገሩ፡፡

የቦንጎ የበኩር ልጅ ኑረዲን ቦንጎ ቫለንቲን እና የቀድሞ የፕሬዚዳንት ቃል አቀባይ ጄሲ ኤላ ኤኮጋ በሙስና ወንጀል ተከሰው በጊዜያዊ እስር ላይ ይገኛሉ ሲል የሊብሬቪል አቃቤ ህግ አንድሬ-ፓትሪክ ሮፖናት ተናግረዋል፡፡

ከእ.ኤ.አ ከ2009 ጀምሮ በነዳጅ የበለጸገቸውን ማዕከላዊ አፍሪካ አገር ሲመሩ የቆዩት የ64 ዓመቱ ቦንጎ፣ በፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አሸናፊ መሆናቸውን ካወጁ በኋላ ባለፈው ነሐሴ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ተወግደዋል፡፡

መፈንቅለ መንግሥቱ በተካሄደበት ዕለት ወታደራዊ መሪዎቹ አንዱን የቦንጎን ልጅ እና ሌሎች አምስት ከፍተኛ የካቢኔ አባላትን ማሰራቸው ይታወሳል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG