በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአፍሪካ ቀንድ ምጣኔ ኃብት


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

ሶማሊላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የንግድ ግንኙነት ለማሻሻል ያለመው የአንድ ዓመት ፕሮጀክት እያለቀ ባለበት በአሁኑ ጊዜ ተጨማሪ ዕርዳታ የሃገሪቱን ምጣኔ ሃብት ያሳድጋል፤ ከእአአ 2018 ጀምሮ ፈጣን ለውጥ እየታየ ባለበት በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ሥፍራ ያጠናክራል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተናግረዋል።

ከፕሮጀክቱ ጀርባ ያለውና ተቀማጭነቱን ለንደን ያደረገው ድርጅት ባሳለፍነው ማክሰኞ መግለጫው ለሶማሊላንድ የኢኮኖሚ መሪዎች የተዘጋጀው የልምድ ልውውጥና ምክክር ፕሮግራም በቅርቡ ይፈፀማል ብሏል።

ይህ ለንግድና ለመዋዕለ ንዋይ ምደባ አስፈላጊነት የሚሠራ ድርጅት ዓላማ በዓለም ድሃ የሆኑ ሃገሮች ተጠቃሚ ሊያደርጋቸው የሚችል የንግድ ግንኙነቶችን እንዲያሳድጉ መርዳት ነው።

ድርጅቱ ከእአአ 2018 ጀምሮም ከኢትዮጵያ ጋር የምጣኔ ሃብት ሥምምነቶችን ማበረታታት በሚቻልበት መንገድ ከሶማሊላንድ መሪዎች ጋር ሠርቷል። ምክክሩ በሁለቱ ወገኖች በኩል የንግድና ትራንስፖርት ሥምምነቶች ረቂቅ ሕግ እንዲዘጋጅ ማስቻሉ ተዘግቧል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG