በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሞቃዲሾ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ የሰው ህይወት አለፈ


ሶማልያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ውስጥ ዛሬ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ፣ በትንሹ 17 ሰዎች መሞታቸውን የሐኪም ቤት ምንጮች ለቪኦኤ ገለፁ።

የሞቃዲሾ ትልቁ ሆስፒታል ዳይሬክተር ዶ/ር ሞሓመድ ዩሱፍ እንደገለፁት፣ ሌሎች 28 ቁስለኞች ሐኪም ቤት ገብተዋል።

አደጋው የደረሰው አንድ ተጠርጣሪ አጥፍቶ ጠፊ፣ ይጓዝባት የነበረችውን ተሽከርካሪ፣ ሕዝብ በሚበዛበት የሞቃዲሾ አውራ-ጎዳና መጋጠሚያ ላይ በማፈንዳቱ እንደሆነም ተገልጿል። ለፍንዳታው አል-ሻባብ ኃላፊነት መውሰዱንም አስታውቋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG