በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሶማሊያ ጦር በአል-ሻባብ ላይ ጥቃቱን ቀጥሏል

ፎቶ ፋይል - የሶማሊያ ወታደሮች በሞቃዲሾ
ፎቶ ፋይል - የሶማሊያ ወታደሮች በሞቃዲሾ

የሶማሊያ ጦር ትናንት ባደረገው ጥቃት 100 የሚሆኑ የአል-ሻባብ ተዋጊዎችን መግደሉን አስታውቋል። የአይን እማኞች ከበድ ያለ ውጊያና የአየር ጥቃት እንደነበር ተናግረዋል።

የቪኦኤው ሞሃመድ ዳይሴን ከሞቃዲሹ እንደዘገበው፣ በሃገሪቱ ማዕከላዊ ግዛቶች በተወሰደው ጥቃት ከመቶ በላይ የአል-አባብ ተዋጊዎች ተገድለዋል።

በአል-ሻባብ ላይ ጥቃቱ የተደረገው በአካባቢው ሚሊሻዎች እገዛ እንደነበር የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አብዱላሂ አሊ ተናግረዋል።

ከባድ ውጊያና አል-ሸባብ ላይ ያነጣጣረ የአየር ጥቃት እንደተፈጸመ ለቪኦኤ በስልክ የተናገሩ ነዋሪዎች አስታውቀዋል።

ባለፈው ሳምንት በሞቃዲሹ ሁለት በመኪና ላይ የተጠመዱ ፈንጂዎች 120 ሰዎችን ገደለው ከ300 በላይ ማቁሰላቸው ይታወሳል።

This item is part of
XS
SM
MD
LG