በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሶማሊያ ጦር በአል-ሻባብ ላይ ጥቃቱን ቀጥሏል


ፎቶ ፋይል - የሶማሊያ ወታደሮች በሞቃዲሾ
ፎቶ ፋይል - የሶማሊያ ወታደሮች በሞቃዲሾ

የሶማሊያ ጦር ትናንት ባደረገው ጥቃት 100 የሚሆኑ የአል-ሻባብ ተዋጊዎችን መግደሉን አስታውቋል። የአይን እማኞች ከበድ ያለ ውጊያና የአየር ጥቃት እንደነበር ተናግረዋል።

የቪኦኤው ሞሃመድ ዳይሴን ከሞቃዲሹ እንደዘገበው፣ በሃገሪቱ ማዕከላዊ ግዛቶች በተወሰደው ጥቃት ከመቶ በላይ የአል-አባብ ተዋጊዎች ተገድለዋል።

በአል-ሻባብ ላይ ጥቃቱ የተደረገው በአካባቢው ሚሊሻዎች እገዛ እንደነበር የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አብዱላሂ አሊ ተናግረዋል።

ከባድ ውጊያና አል-ሸባብ ላይ ያነጣጣረ የአየር ጥቃት እንደተፈጸመ ለቪኦኤ በስልክ የተናገሩ ነዋሪዎች አስታውቀዋል።

ባለፈው ሳምንት በሞቃዲሹ ሁለት በመኪና ላይ የተጠመዱ ፈንጂዎች 120 ሰዎችን ገደለው ከ300 በላይ ማቁሰላቸው ይታወሳል።

XS
SM
MD
LG