ዋሺንግተን ዲሲ —
ዓለምቀፍ ቀይ መስቀል ከየመን ሰባ አንድ ሰራተኞቹን አስወጣ። ጦርነቱ እየተባባሰ በመሆኑና ሰራተኞች ለጥቃት በመጋለጣቸው እንደሆነም አስታውቋል።
ቀይ መስቀል ትናንት ባወጣው መግለጫ በአሁኑ ወቅት የምናካሂደው እንቅስቃሴ እየታገደ ዛቻ እየተሰነዘረብንና በቅርብ ሳምንታት ደግሞ በቀጥታ ዒላማ እየተደርግን ነው ብሉዋል።
ሰባ አንድ ሰራተኞች መውጣታቸው የድርጅቱን የቀዶ ጥገና ህክምና የውሃና የምግብ ዕርዳታ መርኃ ግብሮቹን የሚነካ ይሁን እንጂ አራት መቶ ሃምሳ ሰራተኞቹ አሁንም ሥራቸውን እንደሚቀጥሉ ቃል አቀባይዋ ማሪ ክሌይር ፌጋጋሊ አመልክተዋል።
ባለፈው ሚያዝያ ወር የመን ታኢዝ ከተማ ውስጥ ማንነቱ ያልታወቀ ታጣቂ ተኩስ ከፍቶ አንድ ሊባኖሳዊ የዓለምቀፍ ቀይ መስቀል ሰራተኛ ገድሏል።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ