በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

መንግሥት በትጥቅ ትግል እንደማይሸነፍ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውይይት ጥሪ አቀረቡ


መንግሥት በትጥቅ ትግል እንደማይሸነፍ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውይይት ጥሪ አቀረቡ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:09 0:00

መንግሥት በትጥቅ ትግል እንደማይሸነፍ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውይይት ጥሪ አቀረቡ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኀይሎች፣ መሣሪያቸውን አውርደው ወደ ውይይት እንዲመጡ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ዛሬ ማክሰኞ፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሡት ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት፣ የትኛውም የትጥቅ ትግል የሚያደርግ ኃይል፣ መንግሥትን መገልበጥ አይችልም፤ ብለዋል።

በዐማራ እና በትግራይ ክልሎች መካከል ያሉ አከራካሪ አካባቢዎችን አስመልክቶ፣ መንግሥት በያዘው የሕዝበ ውሳኔ አማራጭ ላይ ውይይት እንደተደረገ ተናግረዋል፤ የተሻሉ ሊባሉ የሚችሉ ሌሎችም የመፍትሔ አማራጮች ካሉ በሩ ክፍት እንደኾነ አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በቅርቡ ስላነሡት የባሕር በር ጥያቄ እና ምላሽ እንዲያገኝ መንግሥታቸው ስለሚከተለው አማራጭም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG