በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በደቡብ ሱዳን የግዳጅ ጋብቻ


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

እንዲቀር ለማድረግ የሚያስችሉ ተጨማሪ ዕርምጃዎች ካልተወሰዱ አንድ የልጃገረዶች ትውልድ ትምህርት ሳያገኝ ሊቀር እንደሚችል፤ ሴቶች በወሊድ ወቅት እጅግ ለበረቱ የጤና ሁከቶች፣ ለፆታና ለቤት ውስጥ ጥቃቶች ሊጋለጡ እንደሚችሉ ኦክስፋም የሚባለው የእንግሊዝ ግብረሰናይ ድርጅት አስጠነቀቀ።

“ለትዳር መወለድ” በሚል ርዕስ ድርጅቱ ትናንት ባወጣው ሪፖርቱ ደቡብ ሱዳን ሴቶች ትምህርት ዕድል ከማያገኙባቸው በመላ ዓለም ካሉ እጅግ አስቸጋሪ የሚባሉ ሃገሮች አንዷ መሆኗን ጠቁሞ፤ በጋብቻ ምክንያት እጅግ የበዛ ቁጥር ያላቸው ልጃገረዶች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ እንደሚገደዱ አመልክቷል።

በቀድሞዪቱ የዩኒቲ ግዛት ከተማ ኒያል ውስጥ ለአራት ተከታታይ ዓመታት አካሂጃለሁ ያለውን ቅኝትና ጥናትና ውጤት ያስመረኮዘው ኦክስፋም፤ ከሰባ ከመቶ በላይ ልጃገረዶች የሚዳሩት ለአቅመ ሄዋን ከመድረሳቸው በፊት መሆኑን አሳውቋል።

በሃገሪቱ ውስጥ እየተካሄዱ ባሉ የርስ በርስ ግጭቶች ምክንያት የተፈጠሩት ረሃብና ድኅነት ብዙ ወላጆች ለጥሎሽ ሲሉ ልጆቻቸውን በጨቅላነታቸው ለመዳር እንዲዳረጉ ያደረጓቸው መሆኑንም የኦክስፋም የደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ራንጃን ፑዲያል ለአሜሪካ ድምፅ ገልፀዋል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG