በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያዊያኑ ሠልፍ በመንግሥታቱ ድርጅት ደጅ


የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና መሥሪያ - ኒው ዮርክ
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና መሥሪያ - ኒው ዮርክ



please wait

No media source currently available

0:00 0:06:47 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ከተለያዩ የሲቪክ ማኅበራትና የፖለቲካ ድርጅቶች የተውጣጡ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያ አሜሪካዊያን ትናንት በኒው ዮርክ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት በኢትዮጵያ ይካሄዳሉ ስላሏቸው የመብት ጥሰቶች የተቃውሞ ሠልፍ አካሂደዋል።

በተለይ የሕዝቦችን ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀል አስመልክቶ፣ የዘር ማጥፋት ወንጀል በኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈፀመ መሆኑን፣ ለዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ለማመልከት እንደሆነ ከሠልፉ አዘጋጅና አስተባባሪዎች አንዱ ለዝግጅት ክፍላቸን ገልፀዋል።

ሕዝቦችን ማፈናቀል ሕገወጥ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ባለፈው ሣምንት ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር መግለፃቸው ይታወሳል።

በኒው ዮርክ በተካሄደው ሠልፍ ላይ የተካፈሉት ከዋሽንግተን ዲ.ሲ.ና አካባቢዋ በሁለት አውቶቡሶችና በአነስተኛ መኪኖች ወደ ከተማዋ የተጓዙና የኒው ዮርክ ከተማ ነዋሪዎች መሆናቸውን አዘጋጆቹ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

ለዝርዝር መረጃ የተያያዘውን ዘገባ ያዳምጡ
XS
SM
MD
LG