በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሰሜን ሸዋ ዞን በቀጠለው ግጭት ሰዎች ተገደሉ


በሰሜን ሸዋ ዞን በቀጠለው ግጭት ሰዎች ተገደሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:38 0:00

በሰሜን ሸዋ ዞን በቀጠለው ግጭት ሰዎች ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደጋም ወረዳ፣ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ በነበረው የተኩስ ልውውጥ፣ ሦስት ሰዎች መገደላቸውንና ሌሎች ሦስት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ።

በአንጻሩ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በፌስቡክ የማኅበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው፣ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ እና ምሥራቅ ጉጂ ዞኖች ውስጥ ወታደራዊ ዘመቻ እያካሔደ ነው። በሰሜን ሸዋ ዞን ስላለው ግጭት ግን ሚኒስቴሩ የጠቀሰው ነገር የለም፡፡ ከሰሜን ሸዋ ዞንና ከደጋም ወረዳ ባለሥልጣናት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረትም ለጊዜው አልተሳካም።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG