በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ወረ ጃርሶ" በተባለ ወረዳ ውስጥ ልጆቻቸው በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለፁ


"ወረ ጃርሶ" በተባለ ወረዳ ውስጥ ልጆቻቸው በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለፁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:28 0:00

"ወረ ጃርሶ" በተባለ ወረዳ ውስጥ ልጆቻቸው በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለፁ

በኦሮምያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን "ወረ ጃርሶ" በተባለ ወረዳ ውስጥ ባለፈው ማክሰኞ ልጆቻቸው በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እንደተገደሉባቸው ሁለት ወላጆች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።

ከሸኔ ታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል የተገደሉትን ልጆቻቸውን አስክሬን ማንሳትና መቅበር አለመቻላቸውንም ገልፀዋል።

በጉዳዩ ላይ የወረዳ ኃላፊዎችን፣ የኦሮምያ ክልል ባለሥልጣናትን እና ከፌደራል መንግሥት ባለሥልጣናት ምላሽ ለማግኘት በየደረጃው ሙከራ ያደረግን ሲሆን ለዛሬ ሳይሳካ ቀርቷል። ምላሻቸውን እንዳገኘን ይዘን እንመለሳለን።

ከቤተሰቦች የተገኘውን መረጃ ፀሐይ ዳምጠው አሰናድታዋለች ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ።

XS
SM
MD
LG