በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ምርጫ ቦርድ ስለሶማሌ ክልል ምርጫ


ፎቶ ፋይል፦ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ
ፎቶ ፋይል፦ ወይዘሪት ሶሊያና ሽመልስ

"ኦብነግ እና ሌሎች ፓርቲዎች ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸው በቀጣዩ የምርጫ ሂደት ላይ ምንም ለውጥ እያመጣም" ሲል ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የቦርዱ የኮሙኒኬሽን አማካሪ ሶሊያና ሽመልስ በሰጡት መግለጫ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን ለመፍታት ከአንድ ወር በፊት ቦርዱ የሚጠበቅበትን ሁሉ ማድረጉን ገልጸው፣ ባሁኑ ወቅት ኦብነግ እና ሌሎች ፓርቲዎች ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸው በምርጫ ሂደቱ ላይ “የውጤትም ሆነ የአሰራር ለውጥ አያመጣም” ብለዋል፡፡

መስከረም 20 ለሚከናወነው የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ቦርዱ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የገለጹት ሶሊያና፣ በምርጫ 2013 በሁለቱም ዙሮች ድምጽ ባልተሰጠባቸው ስፍራዎች ስለሚካሔደው ምርጫ እስካሁን ውሳኔ ላይ ያለመደረሱን አመልክተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

ምርጫ ቦርድ ስለሶማሌ ክልል ምርጫ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:12 0:00


XS
SM
MD
LG