በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ምርጫ ቦርድ የ618 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች እንደደረሱት አስታወቀ


የምርጫ ቦርዱ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ
የምርጫ ቦርዱ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ

ምርጫ ቦርድ ከሚጠብቃቸው 942 አጠቃላይ ውጤቶች መካከል እስካሁን የደረሱት 618 መሆናቸውን አስታወቀ።

ምርጫው በተካሔደባቸው 440 የምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ም/ቤቶች ከሚጠበቀው አጠቃላይ 942 ውጤት ውስጥ ወደ 35 የሚሆኑት ወደ ቦርዱ ማዕከል እንዳልደረሱ የቦርዱ መረጃ ያሳያል፡፡ በ160 የምርጫ ክልሎች ላይ በፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታዎች መቅረባቸውንም ቦርዱ ገልጿል፡፡

ይህን ጨምሮ ቦርዱ የሚያከናውነው የማጣራት ሂደት ውጤት በጊዜ ማሳወቅ እንዳይቻል ማድረጋቸውን የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ምርጫ ቦርድ የ618 ምርጫ ክልሎች ውጤቶች እንደደረሱት አስታወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:57 0:00


XS
SM
MD
LG