መቀሌ —
ኢትዮጵያ “የባህር ኃይል እንዲኖራት ለማድረግ እንቅቃሴዎች ተጀምረዋል” ሲሉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንን አስታውቀዋል።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በመቀሌ ከተማ ውስጥ ዛሬ ባካሄደው መድረክ ላይ የተናገሩት ጄነራል ሰዓረ በአዲሱ ዓመት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታነፀ ሠራዊት ለመገንባት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ለዚህም መንግሥት የተለያዩ አደረጃጀቶችን መቅረፁንና ሥራዎቹ መጀመራቸውን አዛዡ አመልክተዋል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ