No media source currently available
ኢትዮጵያ ውስጥ በመጪው ግንቦት ወር ከ 21 ሺ በላይ ዜጎች የጎርፍ አደጋ ሊደርሰባቸው እንደሚችል የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል፡፡ ከእነዚህ ውስጥም 19 ሺ ያህሉ ከመኖሪያቸው ሊፈናቀሉ ይችላሉም ተብሏል፡፡ የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ደበበ ዘውዴ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡