የሚድሮክ ኢትዮጵያና ሆራይዘን ፕላንቴሽንስ ባለሃብት ሼህ መሃመድ ሁሴን አል አሙዲ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሦስት የመንግሥት የእርሻ ድርጅቶችን ለመረከብ ዛሬ ተፈራርመዋል።
የግዥውን ስምምነት ከሼህ አል አሙዲ ጋር የተፈራረሙት የፕራይቬታይዜሽን እና የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጄንሲ ዳይሬክተር ናቸው፡፡
በጨረታ የተሸጡት ድርጅቶች ሥራቸውን በተሻለ ሁኔታ እንደሚቀጥሉ እምነታቸውን ገልፀዋል።
ዛሬ አዲስ አበባ የተሰጠውን መግለጫ ተከታትሎ እስክንድር ፍሬው ያስተላለፈው ዘገባ ፋይል ተያይዟል፤ ያዳምጡት፡፡