በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የመስቀል ደመራ በዓል - በአዲስ አበባ

መስቀል በየኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች የሚከበር ብሔራዊ በዓል ሲሆን በዓሉ በብሔረሰቦች የተለያየ ስያሜ አለው፡፡

መስቀል በየኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች የሚከበር ብሔራዊ በዓል ሲሆን በዓሉ በብሔረሰቦች የተለያየ ስያሜ አለው፡፡
በሃድያ፣ በወላይታ፣ በዳውሮና ጋሞ "መስቀላ"፣ በከንባታ "መሳላ" በየም "ሄቦ" በጉራጌ "መስቀር" በኦሮሞ "ጉባ" ወይም "መስቀላ" በከፊቾ እና ሻኬቾ "መሽቀሮ" በመባል ሲታወቅ በአማራና ትግራይ “የመስቀል በዓል” ተብሎ ይጠራል፡፡
በ2006 ዓ.ም በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ በተካሄደ 8ኛው የተባበሩት መንግሥታት የሣይንስ የትምህርትና ባህል ማዕከል ዩኔስኮ ጉባዔ ላይ የኢትዮጵያዊ የመስቀል በዓል አከባበር በዓለም ቅርስነት ተመዝግቧል፡፡

ተጨማሪ ይጫኑ

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG