በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከጦርነቱ መቆም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመረቀ


መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከጦርነቱ መቆም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመረቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:36 0:00

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከጦርነቱ መቆም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማሪዎችን አስመረቀ

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ የትግራይ ክልልን መነሻ አድርጎ በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሔደው ጦርነት በሰላም ስምምነት ከቆመ በኋላ፣ የመጀመሪያ የኾነውን የተማሪዎች ምረቃ ሥነ ሥርዐት፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ አከናውኗል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በዕለቱ፣ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ድኅረ ምረቃ ሦስተኛ ዲግሪ ድረስ ትምህርታቸውን በተለያዩ መስኮች የተከታተሉ፣ ከሁለት ሺሕ በላይ ተማሪዎቹን አስመርቋል፡፡

ከሦስት ዓመታት በፊት በ2013 ዓ.ም. መመረቅ ይገባቸው የነበሩ ተማሪዎች በተካተቱበት በዚኹ የምረቃ መርሐ ግብር ላይ፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስተያየት የሰጡ ምሩቃን፣ ከአስከፊው ጦርነት ወጥተው ለዚኽ ቀን በመብቃታቸው ከፍ ያለ ደስታ እንደተሰማቸው ተናግረዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG