በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የማኅበራዊ ሚድያ መዘጋት በመገናኛ ብዙኃን ሥራ ላይ ችግር ፈጥሯል - ባለሞያዎች


 የማኅበራዊ ሚድያ መዘጋት በመገናኛ ብዙኃን ሥራ ላይ ችግር ፈጥሯል - ባለሞያዎች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:51 0:00

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለው ገደብ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠውን መረጃ የማሰባሰብ፤ የማደራጀትና ለሕዝብ ተደራሽ የማድረግ መብት ላይ ችግር መፍጠሩን ገለፀ፡፡

የምክር ቤቱ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታምራት ኃይሉ፣ እርምጃው በተለይም በበይነ መረብ ለሚሰራጩት ሚዲያዎች እንቅፋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ማኅበራዊ ሚድያውን ተጠቅመው የተለያዩ ዝግጅቶችን የሚያቀርቡት አዘጋጆች በበኩላቸው የተጣለው ገደብ ሥራቸው ላይ ጫና መፍጠሩን ይናገራሉ፡፡ በጉዳዩ ዙርያ አስተያየት የተጠየቁ አንድ ባለሞያም በማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩን አስረድተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ ሲሉ ጥሪ ቀርቧል፡፡

XS
SM
MD
LG