በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኤድዋር ፊሊፕ የፈረንሣይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ


ፕሬዚዳንታዊ ሥልጣናቸውን ትናንት የተረከቡት ኢማኑኤል ማክሮን ቀኝ ዘመሙን ኤድዋር ፊሊፕን የፈረንሣይ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ፡፡

ፕሬዚዳንታዊ ሥልጣናቸውን ትናንት የተረከቡት ኢማኑኤል ማክሮን ቀኝ ዘመሙን ኤድዋር ፊሊፕን የፈረንሣይ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ፡፡

46 ዓመት ዕድሜአቸው ላይ የሚገኙት ፊሊፕ ሎ አርቭ የምትባለው ወደብ ከተማ ከንቲባና እንደራሴም ሆነው ያገለገሉ ሲሉ የሪፐብሊካን ፓርቲው ለዘብተኛ የሚባለው ክንፍ ወገን የሆኑ ፖለቲከኛ ናቸው፡፡

በ39 ዓመት ዕድሜአቸው የፈረንሣይ ፕሬዚዳንት የሆኑት ኢማኑኤል ማክሮን መንበረ-ሥልጣኑን በይፋ የተረከቡት ትናንት ዋና ከተማዪቱ ፓሪስ ላይ በተካሄደ ደማቅ የተባለ ሥነ-ሥርዓት ነበር፡፡

ፕሬዚዳንት ማክሮን በቃለ-መኃላ ንግግራቸው ላይ በአውሮፓና በዓለምም የፈረንሣይን ቦታ መልሰው እንደሚያስከብሩ፤ ሃገራቸው ከሽብር ፈጠራ ጋር የያዘችውን ፍልሚያም እንደሚቀጥሉ ቃል ገብተዋል፡፡

ማክሮን ባለፈው ሣምንት በተካሄደው የፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ሁለተኛ ዙር ድምፅ ያሸነፉት ፀረ-አውሮፓ ኅብረትና ፍልሰተኛ ጠል የሆኑትን ቀኝ አክራሪ ዕጩ ማሪን ሎ ፔን አሸንፈው ነው፡፡

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG