በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለስ አስታውቋል ኢትዮጵያውያን 43 ሺሕ ዶላር አሰባስበውለታል


인도네시아 반다르람풍의 마을에서 매년 열리는 해안가 청소 행사에서 아이들이 쓰레기를 줍고 있다. 
인도네시아 반다르람풍의 마을에서 매년 열리는 해안가 청소 행사에서 아이들이 쓰레기를 줍고 있다. 

የ26 ዓመቱ ፈይሳ ሌሊሳ በትናንትናው በሪዮ ኦሎምፒክ የወንዶች ማራቶን የብር ሜዳልያ ያሸነፈበትን ሩጫ አጠናቆ ሲገባ በኦሮሞ ተቃውሞ ጊዜ የተጀመረውና በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ የተቃውሞ ምልክት የሆነውን እጅ ማጣመር ምልክት እያሳየ ገብቷል።

ይህን በማድረጉም ወደ ኢትዮጵያ ቢመለስ የግድያ ፣ የእስራት እና ፓስፖርት መቀማት ስጋት ስላለበት ወደ ሀገሩ እንደማይመልስ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ እንደሌሎቹ የኢትዮጵያ አትሌቶች ሜዳልያ ያመጣ ብሄራዊ ጀግና ነው፤ ሃሳቡን በነጻነት መግለጽ ይችላል፤ ወደ ሀገሩ ቢመለስ ምንም ዓይነት ጉዳት አይደርስበትም ብሏል።

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በበኩሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ሁሌም ስለሚዋሽ በምን አምነዋለሁ? ብሏል።

በሌላ በኩል በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ፈይሳ ሌሊሳን የሕግ ድጋፍ እንዲያገኝ በሰዓታት ውስጥ ወደ 43 ሺሕ ዶላር ወይም ወደ 1 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር አሰባስበዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለስ አስታውቋል ፡ ኢትዮጵያውያን 43 ሺሕ ዶላር አሰባስበውለታል
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:25 0:00


XS
SM
MD
LG