በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የቤተሰብ ምጣኔ ጉባዔ ለንደን ላይ ይካሄዳል


በኢትዮጵያ በየዓመቱ 2.6 ሚሊየን ሕፃናት የሚወለዱ ቢሆንም ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር ቁጥሩ እየቀነሰ የምጣቱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥነ-ሕዝብ ጉዳይ ፅ/ቤት ከእንግሊዝ መንግሥት እንዲሁም ከቢልና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የቤተሰብ ምጣኔ ስብሰባ ለዘርፉ ከፍተኛ ገንዘብ ያስገኛል ተብሎ ተጠብቋል፡፡

ለንደን ላይ በሚካሄደው የቤተሰብ ምጣኔ ስብሰባ ላይ የሚገኙት የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም የኢትዮጵያን ልምድ እንደሚያካፍሉ ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

ለዚሁ ስብሰባ ዝግጅት ሲባል አዲስ አበባ ላይ በተዘጋጀው አውደ ጥናት ላይ የተገኙት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከሰተብርሃን ኢትዮጵያ ከቤተሰብ ምጣኔ አንፃር መሻሻል እያሣየች መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዝርዝሩን ከእስክንድር ፍሬው ዘገባ ያዳምጡ፡፡

(ገፁ ሲከፈት የተደራረቡ ወይም የተረበሹ ድምፆችን የሚሰሙ ከሆነ ከማጫወቻዎቹ አንደኛውን ብቻ አስቀርተው የቀሩትን ያቁሟቸው፡፡)


XS
SM
MD
LG