የአሜሪካ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ የአፍሪካ ምኒስትሮች፣ ኢንቨስተሮች፣ የግል ገንዘብ አበዳሪዎች፣ እንዲሁም የአገልግሎትና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ዓመታዊ ለሆነውና በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ በሚያተኩረው ጉባኤ ላይ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ዲሲ ተገናኝተው ነበር።
“መፃኢው የአሜሪካ እና የአፍሪካ የኅይል ትብብር” በተሰኘ መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ፣ በአዲሱ የትረምፕ አስተዳደር የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የግል ኩባንያዎች የአፍሪካን የኤሌክትሪክ ኅይል ልማት፣ መሠረተ ልማት እንዲሁም የማዕድን ሃብትን በተመለከተ ያላቸውን ተሳትፎ እንደገና ለማዋቀር፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናትና የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ተወካዮች መክረዋል።
የቪኦኤው አንተኒ ላብሩቶ ያጠናቀረውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም