በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቆቦ ውስጥ ስድስት መቶ ሰው እንደተገደለ ነዋሪዎች ተናገሩ


የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት የፈረጀው የህወሓት ታጣቂዎቹ በሰሜን ወሎ በቆቦ ከተማና አካባቢው ከ6 መቶ በላይ ሰላማዊ ሰዎችን መግደላቸውን እና ሌሎች አስከፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችም ፈጽመዋል ሲሉ የድርጊቱ ሰለባዎች መሆናቸው የተናገሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ በስልክ ገለፁ።

ጉዳዩን አስመልክቶ መረጃ ያለው መሆኑን የገለጸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በበኩሉ ሁኔታው በእጅጉ እንዳሳሰበው አስታወቀ። እጅግ የበዛ ሰውም ከአካባቢው እንደተፈናቀለ የዓይን ምስክሮች ተናግረዋል።

በጉዳዩ ላይ ከህወሓት ወገን እስካሁን የተገኘ ቀጥተኛ ምላሽ የለም። ሆኖም ክልሉን በመምራት የሚገኙት ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ድርጅታቸው

“የትግራይ መከላከያ ኃይሎች” በሚል የሚጠራቸው ታጣቂዎች በሰላማዊ ዜጎች ላይ እንዲህ ያሉ ድርጊቶችን እንደማይፈፅም ገልፀው፤ በተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡባቸው ውንጀላዎች በገለልተኛ አካላት እንዲጣሩላቸው ጠይቀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

ቆቦ ውስጥ ስድስት መቶ ሰው እንደተገደለ ነዋሪዎች ተናገሩ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:43 0:00


XS
SM
MD
LG