በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የ United States የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርና ከኢጋድ መሪዎች ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ


ጆን ኬሪና የኢጋድ መሪዎች
ጆን ኬሪና የኢጋድ መሪዎች

please wait

No media source currently available

0:00 0:06:23 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጆን ኬሪ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝን ተቀብለው ሲያነጋገሩ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከኛ ጋር በጣም ብዙ ሰርተዋል ብለዋል።

“ በኢትዮጵያ ስላለው የጤና ጥበቃ ጉዳይ ብዙ ተነጋግረናል። በደቡብ ሱዳን ያለውን ሂደት ስለማንቀሳቀስ ጉዳይም ተወያይተናል። ኢትዮጵያ በተለይም ሀገሮችን በማቀራረብ ተግባር፣ ተኩስ እንዲቆም በማድረግና ተቀናቃኝ ወገኖች ወደ ድርድር እንዲያመሩ በማግባባት ረገድ የመሪነት ቦታ ይዛ ቆይታለች። ሶማልያ ውስጥ በተካሄደው የሽግግር ጉዳይም ኢትዮጵያ ለኛ ቁልፍ ሚና ነው ያላት። ለዚህ ተግባርዋም እጅግ እናመሰግናለን። በእውነቱ የክልሉ መሪ ናት።” ሲሉ አሞግሰዋል።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው የኢትዮጵያና የ United States ግንኙነት እየሰረጸ ሄዷል ብለዋል።

" በአከባቢው ሰላም፣ መራጋጋትና ጸጥታ እንዲሰፍን ማድረግ የወቅቱ የትብብራችን ምሰሶ ነው። ከዛ ሌላ ደግሞ United States እና ኢትዮጵያ የአሜሪካ መዋዕለ-ነዋይ ፍሰት ኢትዮጵያ እንዲገባ አበክረን እየሰራን ነው። በዚህ መድረክና ጉባኤ ላይም ትልቅ እድል አግኘተናል። በሀገሪ መዋዕለ-ነዋይ የማፍሰስ ፍላጎት ካላቸው በርካታ የ United States ኩባንያዎች ጋር ስንሰራ ቆይተናል።" ማለታቸው ተጠቅሷል።

XS
SM
MD
LG