No media source currently available
ኬንያ “በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ ገብታለች” ስትል ሶማሊያ ያቀረበችባትን ክስ አስተባበለች። “‘ኬንያ በቀጣዩ ምርጫ በጁባላንድ አስተዳደር ላይ ጫና ለመፍጠር ጥረት እያደረገች ነው’ ስትል ሶማሊያ ያሰማችው ስሞታ ከእውነት የራቀ ነው” ብሏል የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ። ስለኬንያ አምባሳደር ከሞቃዲሾ መባረር የደረሰው ኦፊሴላዊ ደብድዳቤ እንደሌለም ሚኒስቴሩ ገልጿል።