No media source currently available
የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዓለም እጅግ ግዙፍ የሚባለው የስደተኞች መጠለያ ሠፈር እንዳይዘጋ ማገዱን የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች አሞግሰዋል። መንግሥት ከሦስት መቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ ስደተኞችን ያስጠለለውን ዳዳብ የሚባለውን መጠለያ ሰፈር እንደሚዘጋ አስታውቆ ነበር። አብዛኞቹ በሠፈሩ ውስጥ የተጠለሉት ስደተኞች ከሶማሊያ የገቡ ሲሆኑ መንግሥቱ ሊዘጋው የወሰነው ለሀገሪቱ ፀጥታ አደጋ ይደቅናል በሚል እንደነበረ ገልጿል።
አስተያየቶችን ይዩ
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ