በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በሁለት መዝገቦች ላይ ውሳኔውን ለማሰማት ሌላ ቀጠሮ ያዘ


ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቃቤ ህግና በተለያዩ ፓርቲዎች አመራር አባላት በእነ አቶ ሃብታሙ አያሌው እንዲሁም በአቃቤ ህግና በኢንተርኔት አምደኞቹ በነሶልያና ሽመልስ መካከል ባለው ክርክር ላይ ውሳኔ ሳይሰጥ ቀረ።

በሁለቱም መዝገቦች ላይ ውሳኔውን ለማሰማት ሌላ ቀጠሮ ይዟል።

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ዛሬ ረፋዱ ላይ እንደተሰየመ ሊመለከት የነበረው በአቃቢ ሕግና በቀድሞው አንድነት አመራር አባላት አቶ ሃብታሙ አያሌው እነ ዳንኤል ሺበሺ በሠማያዊው ፓርቲው አቶ የሺዋስ አሰፋ በዓረናው አቶ አብረሃ ደስታ እንዲሁም በየትኛውም ፓርቲ አባልነት በማይታወቁት አቶ አብርሃም ሰሎሞን መካከል ያለውን የክርክር መዝገብ ነበረ፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በሁለቱም መዝገቦች ላይ ውሳኔውን ለማሰማት ሌላ ቀጠሮ ያዘ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:48 0:00

XS
SM
MD
LG