በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሴቃ ሊሙ ነዋሪዎች ስለታሠሩ ሰዎች ብሦት እያሰሙ ነው


ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርብ ጊዜያት ተቃውሞዎች የተቀሰቀሱባቸው አካባቢዎች /ካርታ ከሮይተርስ የተገኘ/
ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርብ ጊዜያት ተቃውሞዎች የተቀሰቀሱባቸው አካባቢዎች /ካርታ ከሮይተርስ የተገኘ/

ኦሮምያ ክልል ጂማ ዞን የሊሙ ሴቃ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ብዙ ሰዎች እየታሠሩ መሆኑንና የሚያዙትም እጅግ ጠባብ በሆነ ክፍል ውስጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለእሥረኞቹ ስንቅና የጤና አገልግሎት እንደማይደርስ ሌሎችም የበረቱ ችግሮችን እየተጋፈጡ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ቁጥሩ ከሃያ በላይ ሰው ታጉሮበታል ያሉትን የእሥር ሁኔታ ቪኦኤ ያነጋገራቸው ነዋሪ ከመቃብር ቤት ጋር አመሣስለውታል፡፡

ሰዎቹ የታሠሩት “በተራ ወንጀል አይደለም” ያለው የሊሙ ወረዳ ፖሊስ የተያዙትም በኮማንድ ፖስት እንደሆነ ገልጿል፡፡

የወረዳው ፖሊስ ኮማንደር ኢንስፔክተር ተሰማ እንግዳ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል “ሰዎቹ የታሠሩት መንግሥት ያወጣውን ሕግ በመተላለፍ፣ ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት፣ ከአዲስ አበባ መሣሪያ በማምጣትና ሌሎችም ሕገወጥ ተግባሮችን በመፈፀም ነው” ብለዋል፡፡

የጤናና የሕግ አገልግሎቶች እንደሚያገኙና ዘመድ እንደሚጠይቃቸው ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡

ሊሙ ሴቃ ወረዳ ውስጥ የታሠሩ ሌሎችም ሰዎች እንዳሉ ነዋሪዎች ለዝግጅት ክፍላችን ቢጠቁሙም ኢንስፔክተር ተሰማ ግን “ከተጠቀሱት ሃያ ሰዎች ሌላ የታሠረ ሰው የለም” ብለዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የሴቃ ሊሙ ነዋሪዎች ስለታሠሩ ሰዎች ብሦት እያሰሙ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:09 0:00

XS
SM
MD
LG