በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

‘ስፔስ ኤክስ ድራገን’ ከዓለም አቀፍ ጣቢያው ጋር ተገናኘች


ሁለት የአሜሪካ የጠፈር ሳይንቲስቶች እንዲሁም አንድ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስና ሌላ ሩሲያዊ ሳይንቲስት በአለም ዓቀፉ የሕዋ ጣቢያ ላይ በሰላም ማረፋቸውን የአሜሪካው የሕዋ ምርምር ተቋም (ናሳ) አስታውቋል።
ሁለት የአሜሪካ የጠፈር ሳይንቲስቶች እንዲሁም አንድ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስና ሌላ ሩሲያዊ ሳይንቲስት በአለም ዓቀፉ የሕዋ ጣቢያ ላይ በሰላም ማረፋቸውን የአሜሪካው የሕዋ ምርምር ተቋም (ናሳ) አስታውቋል።

ሁለት የአሜሪካ የጠፈር ሳይንቲስቶች እንዲሁም አንድ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስና ሌላ ሩሲያዊ ሳይንቲስት በአለም ዓቀፉ የሕዋ ጣቢያ ላይ በሰላም ማረፋቸውን የአሜሪካው የሕዋ ምርምር ተቋም (ናሳ) አስታውቋል።

ስፔስ ኤክስ ድራገን የተሰኘችው መንኩራኩር ከዓለም አቀፍ ጣቢያው ጋር ዛሬ ዓርብ መግጠሙንም ናሳ አስታውቋል።

ናሳ በለቀቀው ቪዲዮ በዓለም አቀፉ ጣቢያ የነበሩት ባልደረቦቻቸው ለአራቱ ሳይንትስቶች ሞቅ ያለ አቀባበል ሲያደርጉላቸው አሳይቷል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬትሱ የ 41 ዓመቱ ሱልጣን አልነያዲ ለአገሩ ወደ ሕዋ ሲበር ሁለተኛው ሰው ሲሆን፣ ለኤምሬቷ ከአሜሪካ ምድር ላይ የመጠቀ የመጀመሪያው ሆኗል።

አዲሶቹ የሕዋ እንግዶች ለስድስት ወራት ሲቆዩ፣ 200 የሚሆኑ ሳይንሳዊ ሙከራዎችንና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይፈትሻሉ። በዓለም አቀፉ ጣቢያ ያሉትን ሳይቲስቶች ቁጥርም ወደ 11 አሳድገዋል።

XS
SM
MD
LG