በእስራኤል እና በሐማስ መካከል የተደረሰው የጋዛ ጦርነት የተኩስ አቁም ድርድር፣ በተቃራኒ ዘላቂ ፍላጎቶች የተወሳሰበ ነው፤ ሲሉ ሁለት ምሁራን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
በታጋቾች እና እስረኞች ልውውጥ ላይ በተመሠረተ የተኩስ አቁም ድርድር ላይ ባለው በጋዛው ጦርነት፣ በሁለቱም ወገኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ምሁራኑ አመልክተዋል፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፍትሔ ማግኘት ይቻላል የሚል እምነት እንደሌላቸውም ገልጸዋል።
በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የሴማዊ ቋንቋ መምህር የኾኑትን ዶር. አንበሴ ተፈራንና ዶ.ር አደም ካሚልን አነጋግረናል። ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
መድረክ / ፎረም