በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አይኤስ የቱርክ ወታደሮችን አቃጥሎ ገደለ


/ፎቶ ፋይል/
/ፎቶ ፋይል/

እሥላማዊ መንግሥት ነኝ የሚለው የሽብርና የሁከት ቡድን ሁለት ቱርካዊያን ወታደሮችን ከነሕይወታቸው አቃጥሎ ሲገድል የሚያሣይ የቪድዮ ምሥል ትናንት አውጥቷል፡፡

መሠረቱ ዩናይትድ ስቴትስ የሆነው የክትትል ቡድንና መገናኛ ብዙኃን ባወጡት ዘገባ አሌፖ የሚገኘው የሽብር ቡድኑ ክፍል ሁለቱን ወታደሮች ከያዘበት የብረት መቆለፊያ አውጥቶና በሰንሰለት አሥሮ እሣት ለቅቆባቸዋል፡፡

ባለፈው ወር ውስጥ ሰሜን ሦሪያ ውስጥ በተከፈተ ጥቃት ላይ የተሠለፉ ሁለት የቱርክ ወታደሮችን ይዞ እንደነበረ ቡድኑ ተናግሮ ነበር፡፡

የቱርክ ወታደራዊ ባለሥልጣናትም በአካባቢው ካሠማሯቸው ሁለት ወታደሮቻቸው ጋር የነበራቸው ግንኙነት መቋረጡን በወቅቱ ገልፀው እንደነበር ታውቋል፡፡

XS
SM
MD
LG