በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢራን ጋዜጠኞችን በማሰር ተወነጀለች


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

ጋዜጠኞች ማሠሯን አጠናክራ የቀጠለችው ኢራን በዓለም የፕሬስ ነፃነትን በሚያከብሩ ሠንጠረዥ ላይ ደረጃዋ ይበልጥ ማዘቅዘቁን ዓለምቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ቡድን /Reporters Without Borders/ አስታወቀ።

ዋና ጽ/ቤቱን ፓሪስ ያደረገው ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ትላንት ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ፣ ኢራን ደረጃዋ ከቀድሞ በ6 ወርዶ ከ180 ሃገሮች አሁን 170ኛ ቦታ ላይ ትገኛለች ብሏል።

ኢራን እአአ በ2018 ደረጃዋ ወደ ግርጌ ሊወርድ የቻለውም በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ የሚጠቀሙ ባለሞያና አማተር ጋዜጠኞችን በብዛት ይዛ በማሠሯ መሆኑ ተመልክቷል።

ለጋዜጠኞች መብት ተከራካሪው ቡድን ያወጣው ሪፖርት አክሎም ኢራን በዓለም ጋዜጠኞችን በብዛት ከሚያስሩ ሃገሮች አንዷ ናት ብሏል።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG