ዋሺንግተን ዲሲ —
ከሃኪንግ ቲም የገበያና ሽያጭ ሥራ አስኪያጅ ኤሪክ ሬብ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለ-ምልልስ ከሥር ካለው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ
የኢትዮጵያ መንግሥት የሚንቀሣቀሰው የራሱንም የሌሎችንም ሕጎች ባከበረ ሁኔታ ነው ሲሉ አንድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማት መንግሥቱ ያካሂደዋል ስለሚባለው ዲጂታል ጥቃት ሲጠየቁ መልስ ሰጥተዋል፡፡
ቴክኖሎጂውን ይሸጣል የሚባለው የጣልያን ድርጅት ደግሞ አገልግሎቱ መብቶችን ለመርገጥ እንዲውል እንደማይፈቅድ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት በኢንተርኔት ጥቃት ያካሂዳል ሲል ሂዩማን ራይትስ ዋች የሚባለው የመብቶች ተሟጋች ቡድን ላወጣው ሪፖርት ወገኖቹ ከቪኦኤ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡