በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አሜሪካ ውስጥ ባህላዊ ምግብን ያዘመኑ "የጽዮና ፉድ" መስራችና ባለቤት


አሜሪካ ውስጥ ባህላዊ ምግብን ያዘመኑ "የጽዮና ፉድ" መስራችና ባለቤት
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:25 0:00

አሜሪካ ውስጥ ባህላዊ ምግብን ያዘመኑ "የጽዮና ፉድ" መስራችና ባለቤት

/ ጽዮን በለጠ “የጽዮና ፉድ” መስራችና ባለቤት ናቸው፡፡ እዚሁ የናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሜሪላንድ ሮክቪ የሚገኘው

የንግሥተ ሳባ ኢትዮጵያ ሬስቶራንት" ባለቤት የነበሩት / ጽዮን በለጠ እንደ እንጀራና ወጥ የመሳሰሉ ባህላዊ ምግቦችን ቀለል ባሉ ዘመናዊ አቀራረቦችና እሽጎች አሰናድተው ወደ ትልቁ የአሜሪካ ገበያ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ፡፡

ባህላዊ ምግቦችን እስከነጣዕማቸው በማዘመን በአሜሪካውያን ደንበኞቻቸው ዘንድ ተወዳጅ እንዲሆን እያደረጉ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ የዜና ማሰራጫዎችም ይህንኑ በመግለጽ አድንቀው ጽፈውላቸዋል፡፡

እንደ እንጀራ ክሪስፕና ከምስር የተሰናዱ በርካታ ምርቶቻቸው እንደ ሆል ፉድ፣ ማምስ ኦርጋኒክ እና ዳውሰንስ ማርኬት በተሰኙ ትላልቅ የአሜሪካ የገበያ መደብሮች ውስጥ በተለያዩ ክፍለ ግዛቶች ውስጥ ተሰራጭተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያይዘው ፋይል ያድምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG