አዲስ አበባ —
ኢትዮጵያ በአባይ ላይ የኃይል ማመንጫዎች መሪ ዕቅዷን ተከትላ ግንባታዋን እንደምትቀጥል የውኃ፣ የመስኖና የኃይል ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ አስታውቀዋል።
በካይሮው ውይይት አካሄድና ይዘት ላይ በፅሕፈት ቤታቸው ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ዶ/ር ስለሺ ግብፅ ከተለመደው አሠራርና አካሄድ ውጭ የሆነና የሱዳንን የፖለቲካ ሁኔታ ግምት ውስጥ ያላስገባ ሃሣብ ይዛ ቀርባ እንደነበረ ተናግረዋል።
ይኸው በሦስቱ ሃገሮች መካከል በአባይና በኅዳሴ ግድብ ላይ የሚካሄደው ንግግር ባለፈው ሣምንት እንደገና የተጀመረው ለአንድ ዓመት ያህል ተቋርጦ የከቆየ በኋላ ነው።
የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ