በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በጎንደር ከተማ በአጋቾች የተወሰደችው የ2 ዓመት ህፃን ግድያ ቁጣ ቀሰቀሰ


ጎንደር
ጎንደር

በድጋሚ የታደሰ

በጎንደር ከተማ በአጋቾች የተወሰደችው የ2 ዓመት ህፃን ግድያ ቁጣ ቀሰቀሰ
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:06 0:00

በጎንደር ከተማ ባለፈው አርብ ባልታወቁ ሰዎች ታግታ ከተወሰደች በኋላ ግማሽ ሚልየን ብር ተጠይቆባት የነበረችው የ2 አመት ህፃን በትላንትው እለት መገደሏ ከተሰማ ወዲህ በከተማው ነዋሪዎች ዘንድ ቁጣ ቀስቅሷል፡፡

አጋቾቹ ህፃኗን የገደሏት ወላጆቿ በድርድር እንዲከፍሉ የጠየቁትን 300 ሺ ብር ከተቀበሉ በኋላ ነው:: ዜናውን ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ የከተማዋ ነዋሪዎች አደባባይ ወጥተው ቁጣቸውን አሰምተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ዛሬ ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች በተደጋጋሚ እገታ በሚፈጸምባቸው አካባቢዎች የወንጀል ድርጊቱን ለመከላከል የሚያስችል የመንግስት የጥበቃና ቁጥጥር ሥራ ተግባራዊ እንዲሆን እና እንዲሁም የታጋቾች ደኅንነት እንዲረጋገጥ አሳስበዋል፡፡

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG